መጣጥፎች

1


ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት


ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላምና እዝነት በታላቁ ነብይ


በሙሀመድ በባልደረቦቻቸው እና በቤተሰቦቻቻው ሁሉ ላይ ይሁን፡፡


ከተከበሩት ወራት መካከል አንዱ የሀጅ ወር ዙልሂጃ ነው። ከቀናት ሁሉ


አላህ ዘንድ የተወደዱት ደግሞ አስሩ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው። እንደዉም


ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያለቸው እነኝህ ቀናት ናቸው። የአላህ መልዕክተኛ


እንዲህ ብለዋል፤


عن جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللهِ رَضِيَ الله عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولَ اللهِ صَلَّى الله عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ


٢٨ ، رقم ١١٢٨ ) قال / الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". أخرجه البزار كما فى كشف الأستار ( ٢


.( ١٧ ) : رجاله ثقات ، وصححه الألباني (صحيح الجامع ، رقم ١١٣٣ / الهيثمي ( ٤


ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ


እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ


የዙልሂጃ ቀናት ናቸው » አልበዛር እና አልሐይሰሚይ ዘግበዉታል


አልባኒም ሰሂህ ብለዉታል (ሰሂሁል ጃሚዕ 1133)


عن ابن عباس رضي الله عنهما، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: "ما من أيام العمل الصالح


فيهن أحب إلى الله منه في هذه الأيام العشر. قالوا ولا الجهاد في سبيل الله !! قال : ولا الجهاد


في سبيل الله، إلا رجل خرج بنفسه وماله ولم يرجع من ذلك بشيء" أخرجه البخاري


ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «በነዚህ


አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸም መልካም ስራዎች በበለጠ መልካም ስራዎች


አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ


የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ


ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።»


ቡኻሪ ዘግበውታል


በነዚህ ቀናቶች ትኩረት ልንሰጣቸው ከሚገቡ የዒባዳ አይነቶች መካከል፤


1. ጾም፤ ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ


የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ


እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም)


2


2. ዚክሮችን ማብዛት፤ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣


ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን


ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች


ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል።


عن عبد الله بن عمر رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال : "ما


من أيام أعظم عند الله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأكثروا


7وصحّح إسناده أحمد شاكر / فيهن من التهليل والتكبير والتحميد" أخرجه احمد 224


ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ ه እንዲህ ብለዋል፤


«ከእነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም


ስራ እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ስለዚህ ተህሊል ተክቢር


እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል አህመድ ሻኪርም


ሰሂህነቱን አረጋግጠዋል።


ከተክቢር አደራረግ መካከል፤


الله أكبر ، الله أكبر لا إله إلا الله ، والله أكبر ولله الحمد


“አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር


ወሊላሂልሀምድ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎችም ይዘቶች አሉት።


በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች


ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች ማካከል ነው። ሰዎችን


ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር


ማድረግ ያስፈሊጋል። ዓብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ


አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ


ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ይህም፤ ሁሉም ሰው የራሱን


ዚክር ያደርጋል ማለት ነው እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ


ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም። ይህ መረጃ ያልተገኘለት ውድቅ ስራ


ነው።


3. ሐጅና ዑምራ፤ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች


መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት የሐጅ ዒባዳ


3


ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ


የአላህ መልዕክተኛ ه ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤


عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعت ه يقول: "الحج المبرور ليس له جزاء


إلا الجنة" متفق عليه.


ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ ه እንዲህ


ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ


አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና


ሙስሊም ተስማምተውበታል


4. ኡድሂያ- በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን


በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው።


የሚከተሉት ነጥቦች አጠር ያለ ግንዘቤን የሰጣሉ፤


- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ ه ሱናዎች መካከል ነው።የነብዩ


ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረጉ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች


መድረስ ነው።


- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ


(ተቅዋ) ነው።


- ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ


ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል።


- ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት


ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ


ኡድሂያን ማረድ ይቻላል።


- ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ


ይታረዱሉ።


- የአላህ መልዕክተኛ ه እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል።


አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ፣ የታመመ


እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም።


- ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን


ወይፈን ወይም በሬ መጋርትም ይቻላል።


- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን


በህይወት ለሌሉ ለቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል።


4


- ኡድሂያውን ለራሱ፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ መከፋፈሉ ሱና ነው።


ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ


ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም።


- በዒድ ቀን ኡድሂያን ለማረድ አስቦ የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና


ጸጉሩን አይቆርጥም። ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህ በሀጅ ላይ ያሉ


ሰዎችን የሚመሳሰልበት ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ይህ የሚመለከተው


የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው። እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ


ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው


ግን አይበላሽም።


የመልካም ስራ በሮች ብዙ ናቸውና የቻልነዉን ሁሉ በመፈጸም ወደ


አላህ መቃረብ ይገባል፤ የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣


ዝምድናን መቀጠል፣ ሰደቃ ማብዛት፣ ሱና ሰላቶችን ማብዛት፣ ቁርዓን


መቅራት፣ ዚክር ማብዛት፣ ዱዓን ማብዛት…ወዘተ ያስፈልጋል።


አላህ በነዚህ ወርቃማ ጊዜያት ከሚጠቀሙና አላህ ዘንድ መልካም


ምንዳን ከሚያገኙ ጠንካራና ብልህ የአላህ ባሮች ያድርገን።


ዝግጅት- አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ



የቅርብ ጊዜ ልጥፎች

መልእክት ከሙስሊም ሰባኪ ለክርስቲ ...

መልእክት ከሙስሊም ሰባኪ ለክርስቲያን ሰው

የሸዋል ስድስት ቀናት መፆም በጎነ ...

የሸዋል ስድስት ቀናት መፆም በጎነት SHAWAL

የተከበረው ቁርኣን ምንድን ነው? ...

የተከበረው ቁርኣን ምንድን ነው?

የመልዕክተኛው ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰ ...

የመልዕክተኛው ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለምን ሱና ተግባራዊ ማድረግ ግዴታ ስለመሆኑና የተቃወመም ከሃዲ መሆኑን በተመለከተ